Notifications

No notifications
We will send an invite after you submit!
  • Helping hands

    In lieu of flowers

    Please consider a donation to Breast Cancer Awareness.
  • Help keep everyone in the know by sharing this memorial website.

Memories & condolences

Year (Optional)
Location (Optional)
Caption
YouTube/Facebook/Vimeo Link
Caption
Who is in this photo?
Or start with a template for inspiration
Cancel
By posting this memory, you agree to our Terms of Service and Privacy Notice.
This site is protected by reCAPTCHA and the Google Privacy Policy and Terms of Service apply.
Helping hands

In lieu of flowers

Please consider a donation to Breast Cancer Awareness.

My deepest condolences to her family and friends! Her life is well lived, and she needs to rest in peace! Let go  Muluberhan, let go Colonel; Let go.....

Comments:
  • Please make sure you've written a comment before it can be published. If you prefer to remove your comment, you can delete it.
  • Sorry, we had some trouble updating your comment.

ሰማይ ተከፈተ

ሰማይ ተከፈተ ማሕሌት ተሰማ

ዝማሬ መላእክት ያለው ልዩ ዜማ

ከሱራፌል መሐል አብራ ተቀላቅላ

አንድ ድምፅ አብራ አለች ያላት ልዩ ቃና

ከምትወደው አምላክ ከፊቱ የቆመች

በጣም የምንወዳት በጣም የምትወደን ዛሬ አንድ ነፍስ አለች

በነጩ ዙፋን ፊት በደስታ የቆመች

በምትወደው ዜማ እያሸበሸበች

ከእርሱ ፊት የቆመች ይቺ ነፍስ የማነች

በምድራዊ ሕይወት ምን አይነት ነበረች

ምን አረጋ ምን ሠርታ ለዚህ ክብር በቃች

ከፀዳለ ማርያም የሕይወት ማሕደር

ከሠራችው ሁሉ ጥቂት ሲመረመር

ጎልቶ የሚወጣው ያበቃት ለክብር

ምስጋናና፤ ዕምነት፤ ጽናትና ፍቅር

አነዚህን አይተናል ቆማ ስትመሰክር

እምነቷ ልዩ ነው ወደርም የሌለው

ከቅዱሳን ተራ ነው ሚደመረው

ፅናቷም እንዲሁ ምንም አቻ የለው

እንደወርቅ በእሳት ነው ተፈትኖ ያለፈው

የጻድቃን ሰማዕታት ታሪክ ሲነገረን

ተረት ተረት እንጂ እውነት የማይመስለን

ይኸው እንድናምን አምላክ እርሷን ሰጠን

አይተናል ቀን በቀን ስትኖር ይህንን

ሰለስቱ ደቂቅ እንዳመሰገኑ በእሳት ውስጥ ሆነው

የማሕሌት ምስጋና ከቶ የማያልቅ ነው

የዝማሬው ቃና ከአፏ የሚፈሰው

ከነዳዊት ጎራ የሚደምራት ነው

ከሁሉም የሚበልጥ የማሕሌት ነገር

አብልጦ የሰጣት ወርቅ የሆነ ፍቅር

ብዙ ብዙ ፍቅር

ከማዕረጋተ ነፍስ ከቁንጮው ላይ ያለው

አምላክን ፊት ለፊት ለማየት የሚያበቃው

ትልቁ ችሎታ መውድ ነው ፍቅር ነው

ሃጥኡን ፃድቁን እኩል የወደደ

አምላክን ለማየት እርሱ ነው የታደለ

ከማሕሌት መለየት በጣም የሚከብደው

እያንዳንዳችንን ስለመትወደን ነው

ተቀድቶ የማልቅ ከእርሷ የሚፈሰው

ለትሽ ትልቁ ፍቅሯ እኩል ነው

ታዲያ ለዚች ነፍስ ምን እናድርግላት

እኔ እንደሚመስለኝ የሠጠችን ፍቅር መልሰን ብንሰጣት

በፀሎት በዜማ በክብር ብንሸኛት

ከዚህ አለም አሻግሮ አምላክ ፊት ያቁማት

ከቅዱሳን ጋራ አብሮ ይደምራት

Comments:
  • Please make sure you've written a comment before it can be published. If you prefer to remove your comment, you can delete it.
  • Sorry, we had some trouble updating your comment.
በሆነ የሚገርም አጋጣሚ አንቺ ብቻ በምታውቂው …
2009, Virginia
በሆነ የሚገርም አጋጣሚ አንቺ ብቻ በምታውቂው ምክንያት "የሰው ሰው" የሚለውን መለያ/ቅፅል ስም ሰጥቼሽ አንቺም ተቀብለሽ ለ12 አመታት እስከመጨረሻዋ ሰአት "ማህሌት" የሚለው ስምሽ እስከሚጠፋኝና የሌላ ሰው መጠሪያ እስከሚመስለኝ ድረስ መጠሪያሽ አደረኩት:: ዛሬ ላይ ሆኜ የሠራሽውን መልካም ሥራ..የተጋደልሽውን ገድል ... የቀደድሽውን ፈር... ዞር ብዬ ሣየው እውነትም ትክክል ነበርኩኝ... "የሰውም ሰው" ነበርሽ!! ምርጥ ዘር!! የዘራሽው ይብቀል!!
Comments:
  • Please make sure you've written a comment before it can be published. If you prefer to remove your comment, you can delete it.
  • Sorry, we had some trouble updating your comment.

ምን እንደምል ግራ ገብቶኛል

ማሒ የዘመናችን ድንቅ ጀግና ወጣት እንደነበረች 

ከአንደበቷ ለመረዳት ብዙም አላዳገተኝም 

በመጨረሻው ሰአት ያስተላለፈችው መልእክት በእውነቱ  የሚደንቅ ነው እንዲህ አይነት ጥንካሬ እና ልበሙሉነት ሰው አለው ብዬ አልገምትም ነበር በእውነት ጀግና እና አስተማሪ ወጣት ነው ያጣነው

ነፍስ ይማር

የታባቱ ሞትም ይሙት!!

° ° ° °

እባካችሁ ዘመዶቼ -

ስሞት ሞትም አብሮኝ ይሙት፣

በሳቅ በደስታ ግደሉት፣

በሃሴት በዕልልታ ውገሩት፣

እባካችሁ ዘመዶቼ-

ለሞት የልብ ልብ አትስጡት፣

ናቁት አጥላሉት አውግዙት፣

በሙሾ ግነን አትበሉት፣

በሞቴ፣ እንዳታስደስቱት።

እንደ ዶርዜ ወንድሞቼ፣

በሳቅ ታጅቤ ኮርቼ፣

ሞቴን በዘፈን ሞልቼ፣

በዳንኪራ ሰበቃና፣ በዘፈን ሆይታ አካትቼ፣

በሠርጌ ብቀበር ሞቼ፣

እፀድቅ ነበር ባትረሱ፣

በእንባ ውሌን ባታፈርሱ።

እባካችሁ ዘመዶቼ-

በሳቅ ጉዞ ፍታት ፍቱኝ፣

በሙሾ ዋይታ አታጅሉኝ፤

እናቴም ፊትሽ አይክሰል፣

በእልልታ ብርሃን ይንበልበል፤

በእረፍቴ እንዳታፌዥብኝ፣

በሠርጌ እንዳታለቅሽብኝ።

ገጽሽ በጭንቅ አይወረስ፣

ልብሽ በኅዘን አይላበስ፣

በሆድሽ ሞት አይፀነስ፣

ዕንባ በአይንሽ አይቋጠር፣

የሞት ቅስሙ እንዲሰበር።

አዎን፣ አደራ፣ አደራችሁ፣

የሙት ውሌን ተቀበሉኝ፣

ደስታዬን ተካፈሉኝ፣

ለንስሃ ሞት አይደለም-

ለፍሠሐ እረፍት አብቁኝ፣

ደስታዬን ተካፈሉኝ፣

ለንስሃ ሞት አይደለም-

ለፍሠሐ እረፍት አብቁኝ፤

በዶርዜ እስክስታ አስቀብሩኝ፣

በእልልታው ጉዞ አሳጅቡኝ፣

በጦሩ ችቦ አሳጥሩኝ፣

ጭብጨባችሁ በስልቱ ይውረድ፣

ዛፍ ቅጠሉም አብሮ እስኪረግድ፣

ሀገር ምድሩም ያቅራራ፣

ሀሴት ነው ይበል፣ ጆቢራ፣

ሠርጌ ነው፣ ይምታ ዳንኪራ፣

እንዲህ ስሜት ሲፍለቀለቅ-

ሲፈነድቅ ሲግል ሃሞት፣

ቱማታው ሲዋጥ በላቦት፣

ሆይታ በሆይታ ሲራኮት፣

ማሳለፊያ መግቢያ ሲያጣ፣

ፍርሃት ገበናው ሲራቆት መቃረቢያ ፍንጭ ሲያጣ፣

በእልልታ ሲወገር ብሶት፣

ብቻ ነው፣ ሞት እራሱ የሚሞት።

እባካችሁ ዘመዶቼ-

ሞትም አብሮኝ ይሙት!

በእልልታችሁ ግደሉት፣

በዳንኪራችሁ ዉገሩት፣

ከአጥንቴ በታች ቅበሩት።

ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን፤ ዶርዜ ሰፈር – 1963 ዓ.ም.

     የመንገድ ዳር አበባ
አንቺ ድንቅ አበባ ውበትሽ የሚያምር
መንገድ ዳር መብቀልሽ አለው ልዪ ሚስጥር
ውበትሽን አይቶ ሰው ሁሉ እንዲያደንቅ
ለፈጣሪሽ ጥበብ ሆነሽለት ሰንደቅ
“እንዴት ቢሠራት ነው እንደዚህ ማማሯ?
መንገድ ዳር መብቀሏስ ምን ይሆን ሚስጥሯ?”
ብሎ እንዲጠይቅ ያዬ ሰው በሙሉ
ብርሃን እስከ አለ ታይተሻል ለሁሉ።
ለካ…… ለካ……
ለሙሽራው ጌታ መልዕክተኛው ሆነሽ
ታዳሚን ለመጥራት መንገድ ዳር መቆምሽ
ሠርጉ መደገሱን
ሰዓቱ መድረሱን
እየነገርሽን ነው መጋበዛችንን።
ጩኒዬ አበባዬ ፀዳለ ማሪያም
ድንቅ አድርጎ የፈጠረሽ መድጛኔዓለም
የብሉይ እዮብ ነሽ የአዲስ ኪዳን ጳውሎስ
ጌታ የመረጠሽ መልዕክቱን ለማድረስ
ከሊቅ እስከ ደቂቅ የተደመመብሽ
በእምነት መፅናትን በተግባር የፈፀምሽ
በዚህ በለጋ እድሜ ለእርሱ የመረጠሽ።
ጩኒዬ አበባዬ
አምላክን ማያዬ
በህይወትሽ ማርከሽ በሞትሽ ሰበክሽኝ
በእርሱ ተስፋ እንዳልቆርጥ ፅናት አስተማርሽኝ
ስለሁሉም ነገር እግዜር ያክብርልኝ
የእኔ ተራ ደርሶ እስከምንገናኝ።

ከደረጀ: ቢረሳው
ጳጉሜ 4/2013





Want to see more?

Get notified when new photos, stories and other important updates are shared.
×

Stay in the loop

Mahlet "Chuni" Girma